Mission

 መግቢያ

የምስረታ ታሪክ  የዳይሬክተሮች ፕሬዝዳንት አቶ ዘላለም እሸቱ ከአዋሽ ባንክ ጋር በመተባበር በንግዱ ማህበረሰብ ከብዶ የሚታየውን የስራ ግብር ለማቅለል በየቀኑ እንቆጥብ በሚል በየቀኑ ከነጋዴዎች የስራ ቦታ መድረስ ሲችል፤ በዚህ ሂደት በርካታ የንግዱ ማህበረሰብ መጠቀም እና መገልገል ሲጀምሩ ፤ቁጠባ ብቻ የትም ማድረስ ስለማይችል፤የቀን ቁጠባቸውን ለወርሃዊ ክፍያ እንዲውል በማሰብ ” ቁርሳችንን በመቆጠብ የምንመኘውን አፓርትመንት መገንባት ይቻላል" invest your dejune to build imajination apartment  የሚል ሃሳብ ተወለደ፡፡

ቁርሳችንን በመቆጠብ የምንመኘውን አፓርትመንት መገንባት ይቻላል" የሚለው መፈክር የማህበራችን መሪ ቃል ያረገው  ወርሃዊ ቁጠባችን 1,050 ሲሆን ይህም ለ 30 ቀናት ተካፍሎ 35 ብር ይደርሳል፤በምስረታ ጊዜያት ይህ ገንዘብ ብዙም ሳይደላ ብዙም ሳያንስ ቁርስን ይሸፍን ስለነበረ ነው፡፡