የተከበራችሁ የማህበሩ አባላት በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም በጤና አደረሰን !!!
ደመራ ...................
ደመራው የመስቀል መቆፈሪያ እንጂ የመስቀል መቅበሪያ አይደለም።
እየሆነ ያለው የቱ ነው? ቀበራው ነው?ወይስ ደመራው? በዓመት በዓመት መቅበር እንጂ ማውጣት ከሌለው የደመራው ጥቅም ዘልማድ መሆኑ ነው።
የተቀበረውን ላያወጡ እየደመሩ ማቃጠል ማስመሰል ብቻ ነው።
በደመራው አቃጣዮች አሉ። የተቀበረውን የሚያወጡ ያለውን የማያስቀብሩ ሰዎች ግን የዓመቱ ደመራ ያልገባቸው ይባላሉ።
የዓመት መስቀልን የዓመት ደመራን እያከበርን ሁልጊዜ ያለ የሕይወት መስቀልን የሕይወት ደመራን ከረሳን ቱሪስቶች እንጂ ክርስቲያኖች አይደለንም።
የደመራው ዓላማኮ ያለውን ለመጠበቅ የጠፋውን ለመመለስ የተቀበረውን ለማውጣት ነበር።ደመራችን በተቃርኖ ሲደመር ያለንን ይቀብራል ያጣነውን ያስረሳል።
እሌኒ በደመራዋ መስቀሉን ከተቀበረበት ቆፍራ አውጥታዋለች።
እኛም ወይ የተቀበረውን ቆፍረን እናውጣ ካልሆነ ደግሞ መስቀሉን ለመቅበር አንደምር።
የዘመናችን የመስቀል ጠላቶች ሁልጊዜም ቀበራ ላይ ናቸው።
የመስቀል ወዳጆችስ?
እንኳን አደረሰን !
Recent News